ሶማሊያ እና ሳዑዲ አረቢያ የቀይ ባሕር ደህንነትን ለማጠናከር ያለመ የመከላከያ ስምምነት ተፈራረሙ
15:29 09.02.2026 (የተሻሻለ: 15:34 09.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊያ እና ሳዑዲ አረቢያ የቀይ ባሕር ደህንነትን ለማጠናከር ያለመ የመከላከያ ስምምነት ተፈራረሙ
የመግባቢያ ስምምነቱ በሶማሊያ የመከላከያ ሚኒስትር አህመድ ሞአሊም ፊኪ እና የሳዑዲ አቻቸው ልዑል ካሊድ ቢን ሳልማን መካከል
በሪያድ እንደተፈረመ ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡
ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት በርካታ የጋራ ወታደራዊ እና የመከላከያ ጥቅሞች እንደሚሸፍን ቢገልጽም ዝርዝር ጉዳዮች ይፋ አልተደረጉም።
ስምምነቱ፤ በተለይም በቀይ ባሕር እና በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የባሕር ደህንነት እና ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር እየጨመረ በመጣበት ወቅት በክልላዊ ደህንነት ላይ ያተኮረ ሰፊ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የተፈጠረበት እንደሆነ የሶማሊያ ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X