ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት አፍሪካን በገለልተኝነት አይመለከትም - የማሊ የሕግ ባለሙያ
15:19 09.02.2026 (የተሻሻለ: 15:24 09.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት አፍሪካን በገለልተኝነት አይመለከትም - የማሊ የሕግ ባለሙያ
አይሲሲ ትኩረቱን ዘወትር በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ብቻ በማድረጉ በአፍሪካውያን ዘንድ ተቀባይነቱን አጥቷል ሲሉ የማሊ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት አባል ካዲዲያ ሳንጋሬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
“ምንም እንኳን አይሲሲ ዓለም አቀፋዊ መሆን ቢገባውም በተግባር ግን እንደ ‘የአፍሪካ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት’ ነው እየሠራ ያለው። ፍርድ ቤቱ የአፍሪካ መሪዎችን ብቻ ነው ለፍርድ የሚያቀርበው። ይህ ደግሞ በአፍሪካ መሪዎች ዘንድ እየታየ ላለው ከፍተኛ ጥርጣሬ ምክንያት ሆኗል።”
እንደ ባለሙያዋ ገለጻ፤ በዳርፉር ጉዳይ በኦማር አል-በሽር እንዲሁም በሎረንት ባግቦ ላይ የወጡት የእስር ትዕዛዞች ከባድ ጥያቄዎችን አስነስተዋል።
ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በእነዚህ ግልጽ ድክመቶች ምክንያት ከአይሲሲ ለመውጣት መምረጣቸውንም አንስተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X