ዛሬ በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ የተካሄደው የ"ብስክሌት በአዲስ ፌስቲቫል"
21:35 08.02.2026 (የተሻሻለ: 21:44 08.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዛሬ በአዲስ አበባ አራዳ ፓርክ የተካሄደው የ"ብስክሌት በአዲስ ፌስቲቫል"
ፌስቲቫሉ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ አዋቂዎች፣ ጎብኚዎች፣ ስፖርተኞች እና ታዋቂ ሰዎች ተሳትፈውበታል ተብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ እንዳስታወቀው፣ ፌስቲቫሉ የከተማዋን ውበት በብስክሌት የመቃኘት፣ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ የማስጨበጥ እና ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎችን የማዘውተር ዓላማዎች ተሳክተውበታል፡፡
የከተማዋን የስፖርት ቱሪዝም ፍሰት ለማሳደግ የብስክሌት ውድድሩ ወርሃዊ መርሃ-ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በመዲናዋ በሁለት ዙር በተሠራው የኮሪደር ልማት 241 ኪሎ ሜትር የብስክሌት መንገድ መሠራቱን የትራንስፖርት ቢሮው መረጃ ያሳያል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X








