ግብፅ እና የአረብ ሊግ በሱዳን የሰብአዊ እርዳታ ኮንቮይ እና የሕክምና ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ የአማፂያን ጥቃቶችን አወገዙ
ግብፅ እና የአረብ ሊግ በሱዳን የሰብአዊ እርዳታ ኮንቮይ እና የሕክምና ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ የአማፂያን ጥቃቶችን አወገዙ
ካይሮ በሱዳን የእርዳታ እና የሕክምና ተቋማት ላይ የሚፈጸሙትን "ተደጋጋሚ እና ጨካኝ ጥቃቶች" አውግዛለች። ሚኒስቴሩ በሰሜን ኮርዶፋን በዓለም የምግብ ፕሮግራም የእርዳታ ኮንቮይ ላይ በድሮን በተሰነዘረ ጥቃት የአንድ ረዳት ሠራተኛ ሕይወት ማለፉንና ሌሎች መቁሰላቸውን፣ እንዲሁም ቢያንስ 24 ሰዎችን ለህልፈት የዳረገ ሌላ የተለየ ጥቃት መፈጸሙን ጠቅሷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ መሰል ድርጊቶች ከፍተኛ መፈናቀል እና የምግብ እጥረት ባለበት በዚህ ወቅት የእርዳታ ስራዎችን እንደሚያደናቅፉ ያስጠነቀቀ ሲሆን፣ ሰብአዊ እርዳታ ያለ ምንም እንቅፋት እንዲደርስ እና ሲቪሎች ጥበቃ እንዲደረግላቸው ጥሪ አቅርቧል።
የአረብ ሊግ በበኩሉ ጥቃቶቹን "በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕግ መሠረት የጦር ወንጀል ነው" ሲል አውግዟል። የሊጉ ዋና ጸሐፊ አህመድ አቡል ገሂት ሲቪሎችን ኢላማ ማድረግ እና ሕይወትን ለመቀጠል አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ማቋረጥ የተከለከለ መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ጸሐፊው የተጠያቂነት አስፈላጊነትን እንዲሁም ለዜጎች እና ለእርዳታ ሰራተኞች ሙሉ ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከላይ የተያያዘው ቪዲዮ በሰሜን ዳርፉር በዓለም የምግብ ፕሮግራም ኮንቮይ ላይ የተፈጸመውን ከፍተኛ ጥቃት ያሳያል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X