የመከላከያ ሠራዊት ማዕከላዊ ዕዝ ሰማዕታቱን ለመዘከር በ70 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባውን ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት አስመረቀ
19:45 08.02.2026 (የተሻሻለ: 19:54 08.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የመከላከያ ሠራዊት ማዕከላዊ ዕዝ ሰማዕታቱን ለመዘከር በ70 ሚሊየን ብር ወጪ ያስገነባውን ዲጂታል ቤተ-መጻሕፍት አስመረቀ
ቤተ-መጻሕፍቱ የተገነባው በሰሜኑ ጦርነት መስዋዕት የሆኑ ጀግኖችን ለመዘከር ሲሆን "ሰላም የማዕከላዊ ዕዝ ሰማዕታት መታሰቢያ ዲጅታል ቤተ-መጻሕፍት" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።
በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ መከላከያ ሠራዊቱ አንድ ሕይወቱን ከፍሎ የሃገሩን ሰላም ከማፅናት ባሻገር በልማት ተግባሮች ላይ እኩል ተሳትፎ በማድረግ ትውልድ ለመገንባት እየሠራ ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው፣ ዕዙ ጀግኖቹን ለመዘከር ውጊያን የሚተርክ ሃውልት አልገነባም ምክንያቱም ለትውልዱ እውቀትን እንጅ ጦረኛነትን መስበክ አይፈልግም ብለዋል ሲል መከላከያ በማኅበራዊ የትስስር ገፁ አስነብቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



