ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሚደገፍ ኃይል መሰማራቱን ተከትሎ ከሄይቲ ወታደሮቿን ማስወጣት ጀመረች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
18:32 08.02.2026 (የተሻሻለ: 18:34 08.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኬንያ የተባበሩት መንግሥታት የሚደገፍ ኃይል መሰማራቱን ተከትሎ ከሄይቲ ወታደሮቿን ማስወጣት ጀመረች - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
ኬንያ በሄይቲ የነበራትን ዋናውን የማረጋጋት ተልዕኮ ማጠናቀቋን ተከትሎ፣ ያሰማራችውን የፖሊስ ኃይል ቁጥር እንደምትቀንስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና ጸሐፊ ኮሪር ሲንግኦይ አስታውቀዋል።
እ.ኤ.አ ከጥቅምት 2023 ጀምሮ 735 መኮንኖችን በማሰማራት የ1,000 አባላት ያሉት ሁለገብ የፀጥታ ድጋፍ ተልዕኮ የጀርባ አጥንት ሆና የቆየችው ኬንያ፤ አሁን ቦታውን በተመድ ለሚደገፈው "የቡድን ጥቃት መከላከያ ኃይል" (ጂኤስኤፍ) ታስረክባለች።
የኬንያ ተልዕኮ የሄይቲን ብሔራዊ ፖሊስ ማጠናከሩን፣ ቁልፍ ቦታዎችን ማስጠበቁን እና ዘላቂ ለሆነ ዓለም አቀፍ የፀጥታ ማዕቀፍ መሰረት መጣሉን ሲንግኦይ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።
በተመድ ጠንካራ ውሳኔ የተቋቋመው አዲሱ "ጂኤስኤፍ"፣ በቡድን የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በንቃት ለመከላከል ታስቦ የተዋቀረ ሲሆን፣ ከ5,500 በላይ አባላት ይኖሩታል ተብሎ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X