ኔቶ ከአፍሪካ እንዲወጣ የሚጠይቅ፣ ለጭቁን ሕዝቦች ድጋፍ የሚሰጥ ሰልፍ በፓሪስ ተካሄደ

ሰብስክራይብ

ኔቶ ከአፍሪካ እንዲወጣ የሚጠይቅ፣ ለጭቁን ሕዝቦች ድጋፍ የሚሰጥ ሰልፍ በፓሪስ ተካሄደ

​በሰልፉ ላይ ፍልስጤም ነፃ ትውጣ” እና ሉዓላዊት ሄይቲ” የሚሉ መፈክሮች በከፍተኛ ድምፅ ሲሰሙ ነበር ሲል በስፍራው የተገኘው የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ ገልጿል።

ለስፑትኒክ አፍሪካ አስተያየቱን የሰጠው የሰልፉ ተሳታፊ፣ የጋዛው የሰላም ዕቅድ ግልጽ ማታለል” መሆኑን ገልጿል።

​“ዕቅዱ በቀን 50 ሰዎች ከግብፅ እንዲገቡ እና 150 ሰዎች ማለትም 50 ታካሚዎች እያንዳንዳቸው ሁለት አስታማሚዎችን ይዘው እንዲወጡ የሚፈቅድ ነበር። ነገር ግን፣ በስድስት ቀናት ውስጥ የአንድ ቀን ኮታ እንኳ አልተሟላም። በዚህ መሃል እስራኤል ፍልስጤማውያንን በከፍተኛ ደረጃ መግደሏን ቀጥላለች” ሲል ተቃዋሚው አስረድቷል።

​የሰልፉ አዘጋጆች ቀደም ብለው ባወጡት መግለጫ የሚከተለውን ጥሪ አቅርበው ነበር፦

“እኛ የካሪቢያን፣ የሄይቲ፣ የኩባ፣ የፍልስጤም፣ የቬንዙዌላ፣ የሱዳን፣ የካናኪ፣ የኮሎምቢያ፣ የኮንጎ፣ የፔሩ እና በጦርነት፣ በዘረኝነት እንዲሁም በጭቆና ጠባሳ ያለብን ሕዝቦች በሙሉ፤ ለዓለም ሕዝብ የሕሊና ዳኝነት እና ለጋራ ትግል ጥሪያችንን እናቀርባለን።”

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0