ጊኒ-ቢሳው ከሩሲያ ኩባንያ ጋር ግዙፍ የማዕድን ውል ማጽደቋን የመንግሥት ቃል አቀባይ ገለጹ
19:26 07.02.2026 (የተሻሻለ: 19:34 07.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጊኒ-ቢሳው ከሩሲያ ኩባንያ ጋር ግዙፍ የማዕድን ውል ማጽደቋን የመንግሥት ቃል አቀባይ ገለጹ
የሀገሪቱ የሽግግር መንግሥት ለሩሲያው ሩሳል ግዙፉ የማዕድን ኩባንያ በምስራቃዊ ጋቡ ግዛት የሚገኘውን የቦክሳይት ማዕድን እንዲያለማ ውል መስጠቱን ቃል አቀባይ አብዱራማኔ ቱሬን በመጥቀስ የሀገሪቱ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።
ቁልፍ ዝርዝሮች፦
ፕሮጀክቱ በማዲና ዶ ቦይ ማውጫ (ሳይት) የሚከናወን ሲሆን፣ ከ55 እስከ 90 ሚሊዮን ቶን የሚገመት የቦክሳይት ክምችት እንዳለው ይገመታል።
ስምምነቱ የማዕድን መሠረተ ልማት ግንባታን ያካተተ ነው፤ ሩሳል ቀደም ሲል በጊኒ-ቢሳው የባቡር መስመር እና የወደብ ግንባታ ለማካሄድ ፍላጎት እንዳለው ገልጾ ነበር።
ውሉ የተፈረመው ሁለቱ ሀገራት እ.ኤ.አ. በ2025 መጀመሪያ ላይ በጂኦሎጂ እና ከመሬት በታች ባሉ ሀብቶች ልማት ላይ በጋራ ለመሥራት የተፈራረሙትን የመግባቢያ ሰነድ ተከትሎ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X