በሶማሊያ የእስራኤል ጣልቃገብነት መላውን የአፍሪካ ቀንድና ባሻገር ማስጋቱን የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ገለጹ
19:33 07.02.2026 (የተሻሻለ: 19:34 07.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሶማሊያ የእስራኤል ጣልቃገብነት መላውን የአፍሪካ ቀንድና ባሻገር ማስጋቱን የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ገለጹ
ቀይ ባህር ለዓለም አቀፍ ንግድ ወሳኝ የደም ሥር መሆኑን የገለጹት ሐሰን ሼክ መሐሙድ፣ በደህንነቱ ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት በዓለም ኢኮኖሚ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር አስጠንቅቀዋል።
መሐሙድ፣ በእስራኤል እና ራስ ገዝ በሆነችው ሶማሊላንድ መካከል የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ የሶማሊያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት የሚጥስ "ሕገ-ወጥ እርምጃ" ነው ብለውታል።
ይህ እርምጃ የአፍሪካ ሕብረት ቻርተርን የሚጻረር እና የሀገራትን ብሔራዊ ሉዓላዊነት በማዳከም ረገድ አደገኛ አርአያነት የሚፈጥር መሆኑንም አብራርተዋል።
ፕሬዝዳንቱ የዓለምን ሥርዓት ለመለወጥ የሚደረጉ ሙከራዎችን ያስጠነቀቁ ሲሆን፣ ወደ "የጉልበት አመክንዮ" መመለስ ዓለምን ወደ አለመረጋጋት እንደሚመራት አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X