የአውሮፓ ሚዲያዎች "ፀረ-ሩሲያ" ስልቶቻቸውን በአሜሪካ ላይ እየተጠቀሙ ነው ሲሉ የፑቲን ልዩ መልዕክተኛ ዲሚትሪቭ ገለጹ
16:47 07.02.2026 (የተሻሻለ: 17:34 07.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአውሮፓ ሚዲያዎች "ፀረ-ሩሲያ" ስልቶቻቸውን በአሜሪካ ላይ እየተጠቀሙ ነው ሲሉ የፑቲን ልዩ መልዕክተኛ ዲሚትሪቭ ገለጹ
ኪሪል ዲሚትሪቭ ይህን አስተያየት የሰጡት፣ ከፍተኛ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለሥልጣን ሳራ ሮጀርስ "ፋይናንሻል ታይምስ" ኅዳር 27 ባወጣው ዘገባ መረጃን አዛብቶ አቅርቧል ሲሉ ላቀረቡት ክስ ምላሽ ነው።
የጋዜጣው ዘገባ አሜሪካ በዋሽንግተን የሚደገፉ አመለካከቶችን ለማስፋፋት፣ በአውሮፓ የሚገኙ እና ከ"አሜሪካን ዳግም ታላቅ የማድረግ" ንቅናቄ ጋር ግንኙነት ያላቸውን የጥናት ተቋማት በገንዘብ ለመርዳት አቅዳለች የሚል ነበር።
ሮጀርስ ጋዜጣውን ሲተቹ፤ "መደበኛ የመንግስት ድጋፎች" ከማለት ይልቅ "ምሥጢራዊ ፈንድ" የሚሉ ስሜት ቀስቃሽ ቃላትን መጠቀሙን እና መደበኛ ስራዎችን አጠራጣሪ ከሆነ ምንጭ እንደተገኙ አድርጎ ማቅረቡን ገልጸዋል። ይህም ስልት ብዙ ጊዜ ሴራ በሚጠነስሱ የፖድካስት አቅራቢዎች የሚጠቀሙበት ዓይነት መሆኑን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X