ደቡብ አፍሪካ ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር ውስጥ የተመረተ የእንስሳት የእግር እና የአፍ በሽታ ክትባትን ይፋ አደረገች
13:44 07.02.2026 (የተሻሻለ: 14:04 07.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ ከ20 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር ውስጥ የተመረተ የእንስሳት የእግር እና የአፍ በሽታ ክትባትን ይፋ አደረገች
አገሪቱ ከሽታው ነፃ መሆኗን የሚያረጋግጥ ዓለም አቀፍ እውቅናን መልሳ ለማግኘት ያደረገችው ጥረት አካል መሆኑን ባለሥልጣናት ገልፀዋል፡፡
የመጀመሪያውን ዙር 12,900 በአገር ውስጥ የተመረቱ የእግር እና የአፍ በሽታ* (ኤፍኤምዲ) ክትባቶችን ማሰራጨቷን መንግስት አስታውቋል። ይህ እርምጃ ሀገሪቱ በእንስሳት ጤና ረገድ ራሷን ለመቻል የያዘችውን ስትራቴጂካዊ ለውጥ የሚያሳይ ነው።
ዋና ዋና ዝርዝሮች፦
ይህ በተለያዩ የበሽታው አይነቶች ላይ የሚሰራው ክትባት የተመረተው በመንግስት፣ በግብርና ምርምር ምክር ቤት እና በኦንደርስቴፖርት ባዮሎጂካል ምርቶች መካከል በተደረገ አጋርነት ነው።
የግብርና ሚኒስትሩ ጆን ስቲንሁሴይን እንደገለጹት፣ ይህ ጅምር "በሽታን ከማሳደድ እና ምላሽ ከመስጠት ይልቅ፣ በሳይንስ ላይ የተመሰረተና አስቀድሞ የመከላከል 'የኤፍኤምዲ ጦርነት' ውስጥ መገባቱን" የሚያበስር ነው።
*የእግር እና የአፍ በሽታ (ኤፍኤምዲ) በከብቶች፣ በአሳማዎች እና በበጎች ላይ የሚከሰት ተላላፊ የቫይረስ በሽታ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/