የአዳማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት 2.5 ቢሊየን ብር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን አመረተ
19:30 06.02.2026 (የተሻሻለ: 19:34 06.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአዳማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ባለፉት ስድስት ወራት 2.5 ቢሊየን ብር የሚያወጡ ተኪ ምርቶችን አመረተ
በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ የሚገኙ 19ኙም ሼዶች በውጭና በሀገር ውስጥ ባለሀብቶች የተያዙ ሲሆን፤ ከ9 ሺህ ለሚልቁ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፍጠራቸውም የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በኢኮኖሚ ዞኑ ከሚመረቱ ምርቶች መሃከል፡-
ጨርቃ ጨርቅና አልባሳት፣
የሕንጻና የብረት ቀለም፣
የኮንስትራክሽን ግብዓቶች፣
የመብራት ቆጣሪ እና
የሕጻናት ንጽህና መጠበቂያ ይገኙበታል፡፡
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት 3.4 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ ከቀናት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መናገራቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X