ላቭሮቭ ከስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከአውሮፓ የደህንነትና ትብብር ድርጅት ዋና ጸሐፊ ጋር ያደረጓቸውን ውይይቶች ተከትሎ የሰጧቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦
15:19 06.02.2026 (የተሻሻለ: 15:24 06.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ላቭሮቭ ከስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከአውሮፓ የደህንነትና ትብብር ድርጅት ዋና ጸሐፊ ጋር ያደረጓቸውን ውይይቶች ተከትሎ የሰጧቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦
🟠 በጄኔራል አሌክስዬቭ ላይ የተሰነዘረው የግድያ ሙከራ፤ ኪዬቭ የድርድር ሂደቱን ለማደናቀፍ የታለሙ ተከታታይ ትንኮሳዎችን ለመፈጸም ዝግጁ መሆኗን ያሳያል።
🟠 የአውሮፓ የደህንነትና ትብብር ድርጅትን አስፈላጊነት ጠብቆ ለማቆየት ሊረዱ የሚችሉ እርምጃዎች ከስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ከድርጅቱ ዋና ጸሐፊ ጋር ተወያይተዋል።
🟠 የስዊዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና አሁን ያሉት የአውሮፓ የደህንነትና ትብብር ድርጅት ዋና ጸሐፊ በድርጅቱ ውስጥ ያለውን ቀውስ ለመፍታት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል።
🟠 ሞስኮ ከዋሽንግተን ጋር በስትራቴጂካዊ መረጋጋት ማዕቀፍ ውስጥ ስለ ደህንነት ጉዳዮች ለመወያየት ዝግጁ ነች።
🟠 የ"ኒው ስታርት" ስምምነት ጊዜ ካበቃ በኋላ፣ ሩሲያ ለማንኛውም ክስተት ዝግጁ ነች፤ የስምምነቱ ማብቃት ክፍተት ፈጥሯል።
🟠 ከአሜሪካ ጋር በሚደረገው ውይይት፤ ሩሲያ "የማይከፈል የደህንነት " መርህን ታከብራለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X