"የኒው ስታርት" ስምምነት ማብቃት ‘እየጨመረ ላለው የትርምስ ዓለም ምልክት ነው’ - ተንታኝ
20:07 05.02.2026 (የተሻሻለ: 20:14 05.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
"የኒው ስታርት" ስምምነት ማብቃት ‘እየጨመረ ላለው የትርምስ ዓለም ምልክት ነው’ - ተንታኝ
ሴባስቲያን ፔሪሞኒ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፣ የወታደራዊ ግጭቶች የመባባስ ስጋት “በመላው ፕላኔታችን ላይ በየቦታው” እየታየ ነው፤ የዚህ መሠረታዊ ሰነድ (የኒው ስታርት ስምምነት) ማብቂያም ከዚሁ አሳሳቢ ሁኔታ ጋር የሚገጣጠም ነው።
“ቻይና፣ ሩሲያ፣ አውሮፓ፣ አሜሪካ እና መላው ዓለም በድጋሚ ትጥቅ እያከማቹ ነው ... የዚህ ስምምነት ማብቂያም የጦር መሣሪያ ውድድርን ዳግም ሊቀሰቅሱ ከሚችሉ ሁኔታዎች አንዱ ነው” ብለዋል።
ተንታኙ አክለው፣ ይህ ሁኔታ “እጅግ አደገኛ” መሆኑን ገልጸዋል።
“በ20ኛው ክፍለ ዘመን ሁለት ጊዜ እንዳየነው፣ ዓለም ትጥቅ በምታከማችበት ጊዜ ሁሉ መጨረሻው ዓለም አቀፍ አደጋ ነው” ብለዋል ፔሪሞኒ።
ሩሲያ እና አሜሪካ ከአንድ ሺህ በላይ የኒውክሌር ሚሳኤሎች ወይም ቢያንስ የኒውክሌር የመሸከም አቅም ያላቸው ሚሳኤሎች እንዳሏቸው ጠቁመው፣ ይህም “ፕላኔታችንን 20 ጊዜ ደጋግሞ ለማጥፋት ከበቂ በላይ ነው” ሲሉ አስረድተዋል።
በተመሳሳይ ጊዜ፣ ሺ ጂንፒንግ እና ቭላድሚር ፑቲን ዓለምን በማረጋጋት ረገድ ሚና የመጫወት ፍላጎት እንዳላቸው ማስታወቃቸውን ፔሪሞኒ አመላክተዋል።
በዚህም “ዓለም ከምዕራባውያን ተጽዕኖ እየወጣች መሆኑን" የታዘቡት ተንታኙ፣ ዓለምን ወደ ጥፋት ሊከት የሚችል ያለመመጣጠን ሁኔታን ለማስወገድ አዲስ ዓለም አቀፍ የደህንነት መዋቅር እንዲዘረጋ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X