የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጦር በደቡብ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከ20 በላይ ታጣቂዎችን ደመሰሰ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጦር በደቡብ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከ20 በላይ ታጣቂዎችን ደመሰሰ
የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጦር በደቡብ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከ20 በላይ ታጣቂዎችን ደመሰሰ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.02.2026
ሰብስክራይብ

የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጦር በደቡብ ሱዳን ድንበር አቅራቢያ ከ20 በላይ ታጣቂዎችን ደመሰሰ

​ ስፑትኒክ ካገኘው የማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጦር ኃይል መግለጫ መረዳት እንደተቻለው፣ ሕገ-ወጥ የታጠቁ የወንበዴ ቡድኖች በኦት-ኮቶ ግዛት የድንበር አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ ነበር። እነዚህ ቡድኖች የተፈጥሮ ሀብቶችን በሕገ-ወጥ መንገድ በመዝረፍና በመውሰድ ላይ ተሰማርተው የነበረ ሲሆን፣ በአካባቢው ደህንነት ላይም ስጋት ደቅነው ነበር።

​በአየር የተደገፈው ይህ ወታደራዊ ዘመቻ ከሩሲያ አጋሮች በተገኘ ድጋፍ የታገዙ ክፍሎችን ያሳተፈ ነበር። የጦር ኃይሉ እንደገለጸው፣ ለተዋጊዎች ቅልጥፍና እና ለተኩስ ድጋፍ እንዲውሉ አራት ሄሊኮፕተሮች በሥራ ላይ ውለዋል።

​“የደህንነት ኃይሎች በዘመቻው ቀታና ላይ ሙሉ ቁጥጥር ማድረግ የቻሉ ሲሆን፣ የወንጀለኞች ቡድኖቹ የሚጠቀሙባቸው በርካታ የጦር ሰፈሮች ተገኝተው እንዲወድሙ ተደርጓል” ሲል መግለጫው ጠቅሷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0