ሩሲያ 157 ወታደሮቿን ከዩክሬን ምርኮ አስመለሰች - የመከላከያ ሚኒስቴር
16:19 05.02.2026 (የተሻሻለ: 16:24 05.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ 157 ወታደሮቿን ከዩክሬን ምርኮ አስመለሰች - የመከላከያ ሚኒስቴር
በልውውጡ ምትክ 157 የዩክሬን ጦር እስረኞች ተላልፈው መሰጠታቸውን ሚኒስቴሩ አክሎ ገልጿል።
በተጨማሪም በኪዬቭ አገዛዝ በሕገ-ወጥ መንገድ ተይዘው የነበሩ ሦስት የኩርስክ ክልል የሩሲያ ዜጎች የተመለሱ ሲሆን፣ ወደ ቤታቸው እንደሚሸኙም ተቋሙ አመልክቷል።
የሩሲያ የጦር ኃይል አባላቱ በአሁኑ ወቅት በቤላሩስ የሚገኙ ሲሆን፣ አስፈላጊው እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል። በመቀጠልም ለሕክምና እና ለተሃድሶ ወደ ሩሲያ እንደሚመለሱ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
የሩሲያ ወታደሮች ከምርኮ እንዲመለሱ በሚደረገው ጥረት አሜሪካ ሰብአዊ የአሸማጋይነት ድጋፍ ማድረጓንም ተቋሙ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X