በኮንጎ የተመድ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ (ሞኑስኮ) የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመከታተል ቁርጠኝነቱን አረጋገጠ
18:45 04.02.2026 (የተሻሻለ: 18:54 04.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኮንጎ የተመድ የሰላም አስከባሪ ተልዕኮ (ሞኑስኮ) የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለመከታተል ቁርጠኝነቱን አረጋገጠ
ሞኑስኮ፤ በኳታር አመቻችነት በዶሃ በተደረገው ውይይት በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት እና በኤም23 አማፂያን መካከል ሰኞ ዕለት የተደረሰውን አዲስ የተኩስ አቁም የክትትል ሥርዓት እንደሚደግፍ በድጋሚ አረጋግጧል።
በቡሩንዲ ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ኡቪራ ከተማ የተመድ የሰላም አስከባሪዎች መሰማራት የስምምነቱ ትግበራ የመጀመሪያው እርምጃ ነው። በደቡብ ኬቩ የምትገኘው ይህች ከተማ ባለፈው ታህሳስ ወር በኤም23 አማፂያን ተይዛ የነበረ ቢሆንም፤ ጥር 10 ቀን ግን ወደ መንግሥት ቁጥጥር ተመልሳለች።
የኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ በጥር ወር መጨረሻ ለውይይት ዝግጁ መሆናቸውን በድጋሚ ቢገልጹም፤ "ወንጀለኞች" ካሏቸው ሩዋንዳ እና የኤም23 ቡድን ጋር ድርድር እንደማያደርጉ አስታውቀዋል። ኪጋሊ በበኩሏ በተደጋጋሚ ተሳትፎ እንደሌላት ውድቅ ስታደርግ ቆይታለች።
በተመድ የፀጥታው ምክር ቤት የሩሲያ ልዑክ፤ የውጭ የደህንነት ኩባንያ አባላት በተመድ ካምፕ ውስጥ ተጠልለዋል የሚሉ ዘገባዎችን ተከትሎ ቀደም ሲል ሞኑስኮ ላይ ጥያቄ ማንሳቱ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X