መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ እንደሚያነሳ ተገለፀ
18:49 04.02.2026 (የተሻሻለ: 18:54 04.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ እንደሚያነሳ ተገለፀ
መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ በቀጣዩ ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ እንደሚያቆም መረጃው ደርሶኛል ሲል የሀገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ይህን ተከትሎም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ግብይት በዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ መሠረት እንደሚመራ ዘገባው ጨምሮ ገልጿል፡፡
ውሳኔው በኢኮኖሚ ማሻሻያው መሠረት መንግሥት ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር የገባው ውል አካል ነው ተብሏል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የድጎማ አሠራሩ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለውን የነዳጅ ዋጋ ልዩነት በማስፋት በመንግሥት በጀት ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን በትናንቱ የምክር ቤት ቆይታቸው መናገራቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X