በኦሮሚያ ክልል ሁለት የካንሰር ህክምና ማዕከላት እየተገነቡ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ
18:32 04.02.2026 (የተሻሻለ: 18:34 04.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኦሮሚያ ክልል ሁለት የካንሰር ህክምና ማዕከላት እየተገነቡ መሆኑን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ
በባሌ ሮቤ እና በቡራዩ ከተሞች የሚገነቡት የካንሰር ህክምና ማዕከላቱ ግንባታቸው በቀጣይ ሁለት ዓመት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ እንደሚገቡ የክልሉ የጤና ቢሮ ኃላፊ ነጻነት ወርቅነህ ተናግረዋል፡፡
ማዕከላቱ የካንሰር ህክምና የሚጠይቀውን ከፍተኛ ወጪ እና የአገልግሎት ውስንነቱን ታሳቢ በማድረግ ለማኅበረሰቡ ተደራሽ የማድረግ ዓላማን ያነገቡ መሆናቸን ኃላፊዋ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ገልፀዋል፡፡
በካንሰር የተጠቁ አብዛኞቹ ታማሚዎች ከሀገር ውጪ ተጉዘቅው እንደሚታከሙ እና በክልሉ የጤና ቱሪዝምን ለማስፋፋት እየተሠራ እንደሆነም አንስተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X