የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን የግማሽ ቢሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን የግማሽ ቢሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን የግማሽ ቢሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 04.02.2026
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን የግማሽ ቢሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

ተቋሙ በቅርቡ የተቋቋመውን ኮሚሽን ለማጠናከር ከገንዘብ በተጨማሪ 67.2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሁለት ዘመናዊ ተሽከርካሪዎችን በድጋፍ እንደሰጠ አስታውቋል።

ድጋፉ ኮሚሽኑ የተቋቋመበትን ሀገራዊ የኢነርጂ ፍላጎት የማሟላት ግብ እንዲያሳካና የጀመራቸውን ሥራዎች እንዲያፋጥን ታስቦ የተደረገ መሆኑን የኤሌክትሪክ ኃይል ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮሚሽን ሀገሪቱ ለሰላማዊ ዓላማ የሚውል የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ለመገንባት የያዘችውን ዕቅድ በሕግና በቁጥጥር ማዕቀፍ ለመምራት ጥቅምት 2018 ዓ.ም መቋቋሙ ይታወቃል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0