ለአፍሪካ ኅብረት እንግዶች የኢትዮጵያን ባሕል ለማስተዋወቅ ተዘጋጅተናል - ደ ሊኦፖል ሆቴል
16:21 04.02.2026 (የተሻሻለ: 16:34 04.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ለአፍሪካ ኅብረት እንግዶች የኢትዮጵያን ባሕል ለማስተዋወቅ ተዘጋጅተናል - ደ ሊኦፖል ሆቴል
የአኅጉሪቱ የዲፕሎማሲ መዲና ከየካቲት 4 እስከ 8 ለሚካሄደው 39ኛው ዓመታዊ የአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ዝግጅቷን እያጧጧፈች ነው፡፡ ከዚህ በፊት በተካሄዱት የኅብረቱ ስብሰባዎች ጥሩ ልምድ ያካበተው ደ ሊኦፖል ዓለም አቀፍ ባለ አራት ኮከብ ሆቴል ለጉባኤው የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡
"ከዚህ በፊት በነበረው የአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ወቅት ጥሩ ልምድ ነበረን። አገልግሎታችንን ተጠቅመው፣ ባሕላችንን አይተው ይሄዳሉ። በቀጣይም የነበረውን እርካታ ጠብቀን ለመቀጠል ነው የምናቅደው” ሲሉ የደ ሊኦፖል ሆቴል የሽያጭ እና ማርኬቲንግ ማናጀር ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
ሆቴሉ ከአኅጉሪቱ የተለያዩ ሀገራት ለሚመጡ እንግዶቹ የምግብ ዝግጅት እያደርገ እንዲሁም ከፖሊስ ጋር በመተባበር የጸጥታ ጉዳዮችን ከወዲሁ ዳር ዳር እያሲያዘ እንደሆነም አስረድተዋል፡፡
“ባሕላዊ ለምሳሌ 'ኡጋሊ' እና መሰል ምግቦችን ጨምሮ በሬስቶራንታችን እና በቁርስ አገልግሎታችን ላይ አካትተናል። ሌላው ደህንነት ላይ ነው። ከአካባቢው ፖሊስ ጋር በመተባበር የተለያዩ ስብሰባዎችን እና ሥልጠናዎችን አድርገናል። የራሳችንም ጥበቃ አለን፣ ከመንግሥትም የሚመደብልን ጥበቃ ይኖራል። ሌላው ባሕላችንን ማስተዋወቅ ላይ ነው። ከስታፎቻችን አቀባበል ጀምሮ የቡና ሥነ-ሥርዓት፣ አለባበስ እና የፀጉር አሠራርን ጨምሮ ኢትዮጵያዊ ባሕልን ለማሳየት ተዘጋጅተናል።”
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



