ሴኔጋል በብርቅዬ ማዕድናት ዙሪያ ጥናት ጀመረች
20:28 03.02.2026 (የተሻሻለ: 20:34 03.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሴኔጋል በብርቅዬ ማዕድናት ዙሪያ ጥናት ጀመረች
ሰኞ በዳካር ይፋ የተደረገው ይህ ጥናት የሚከተሉትን ዓላማዎች አንግቧል ተብሏል፦
🟠 የሀገሪቱን የሥነ-ምድራዊ ሀብት አቅም በሰነድ ማደራጀት።
🟠 ዓለም ወደ ታዳሽ ኃይል በሚሸጋገርበት በዚህ ወቅት የማዕድን ዘርፍ ተግዳሮቶችን አስቀድሞ መገመት።
🟠 እነዚህን የማዕድን ሀብቶች ከሴኔጋል ሰፊ የኢነርጂ ስትራቴጂ ጋር ማቀናጀት።
🟠 ጥሬ ዕቃ ከመላክ ባለፈ በሀገር ውስጥ ወደ ማቀነባበር ሽግግር ማድረግ።
ሴኔጋል ከሚታወቁ የማዕድን ክምችቶችዋ በተጨማሪ እስካሁን ያልተነኩ የበርካታ ብርቅዬ ማዕድናት ባለቤት ናት። ለባትሪዎች፣ ለንፋስ ኃይል ማመንጫዎች እና ለፀሐይ ብርሃን (ሶላር) ፓነሎች እጅግ አስፈላጊ የሆኑት ሊቲየም፣ ኮባልት፣ ኒኬል፣ መዳብ እና ማንጋኒዝ ለሀገሪቱ አዳዲስ ዕድሎችን ይዘው መጥተዋል።
ጥናቱን "ፐብሊሽ ዋት ዩ ፔይ" የተሰኘው ጥምረት ከአፍሪካ የአየር ንብረት ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በይፋ አስጀምሯል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X