አፍሪካ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ ተራ ተመልካች ሳይሆን ዕጣ ፈንታዋን በራሷ መወሰን አለባት - ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

ሰብስክራይብ

አፍሪካ በተለዋዋጭ ዓለም ውስጥ ተራ ተመልካች ሳይሆን ዕጣ ፈንታዋን በራሷ መወሰን አለባት - ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ

የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር ይህን ያሉት ዛሬ በዱባይ በይፋ በተጀመረው የዓለም መንግሥታት ጉባኤ ነው።

"ለአፍሪካ ተለዋዋጩ የዓለም ሁኔታ ትልቅ የማንቂያ ደወል ነው። እራሳችንን እንደ ተራ ታዛቢ ሳይሆን የራሳችንን መጻኢ ዕድል እንደምንቀርጽ ግንባር ቀደም አርክቴክቶች እንመለከታለን" ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ በመድረኩ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያን መሠረታዊ ብሔራዊ ጥቅም ከቀጣናዊ አጋርነት ጋር አስተሳስረው አስረድተዋል፡፡

"ለኢትዮጵያ የቀይ ባሕር ኮሪደር ደህንነት ወሳኝ ብቻ ሳይሆን፤ 12 በመቶ የሚሆነው የዓለም የንግድ ልውውጥ የሚያልፍበት በጣም አስፈላጊ መስመር ነው። ይህም ከጠባብ ጂኦ-ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የጸዳ አስቸኳይ የጋራ የትብብር ማዕቀፍ ያስፈልገዋል፡፡"

ከጥር 26 እስከ 28 በዱባይ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከ60 በላይ የዓለም መሪዎች፣ ከ500 በላይ ሚኒስትሮች እንዲሁም ከ80 በላይ ዓለም አቀፍና ቀጣናዊ ድርጅቶች ተገኝተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0