ኢትዮጵያ፤ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት በብዙ የአፍሪካ ሀገራት ማዕከላዊ አጀንዳ ሳይሆን በፍጥነት ዘርፉን ተቋማዊ ለማድረግ ተንቀሳቅሳለች - ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ፤ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት በብዙ የአፍሪካ ሀገራት ማዕከላዊ አጀንዳ ሳይሆን በፍጥነት ዘርፉን ተቋማዊ ለማድረግ ተንቀሳቅሳለች - ዐቢይ አሕመድ

"የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ልማት ከመጀመሪያዎቹ ቅድሚያ ከምንሰጣቸው ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው"፤ አሁን ላይ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት በከፍተኛ የመንግሥት ፖሊሲ ውስጥ ተካቷል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ በዓለም ሁለተኛው የኤአይ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥሉት አንድ ዓመት ውስጥ ተገንብቶ ሥራ እንደሚጀምርም ይፋ አድርገዋል።

“ይህ ዩኒቨርሲቲ አባቶቻችን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ገንብተው ስመጥር እንዳደረጉት ሁሉ ለልጆቻችን ለነገ የተሻለ ዘመን ይዞ ይመጣል።”

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ የኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና ጽሕፈት ቤትን በጎበኙበት ወቅት፤ ተቋሙን ሀገሪቱ በዘርፉ በንቃት እየተሳተፈች እንደሆነ ማሳያ አድርገው መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0