የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል የመጀመሪያውን የህክምና አቅርቦት ማከማቻ መጋዘን በአዲስ አበባ አስመረቀ
17:52 03.02.2026 (የተሻሻለ: 17:54 03.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማዕከል የመጀመሪያውን የህክምና አቅርቦት ማከማቻ መጋዘን በአዲስ አበባ አስመረቀ
አፍሪካ ሲዲሲ የህክምና ቁሳቁሶችን የመግዛት፣ የማከማቸትና በመላው አኅጉሪቱ የማሠራጨት አቅሙን የሚያሳድገውን የመጀመሪያውን ግዙፍ መጋዘን በዛሬው ዕለት በይፋ ማስመረቁን አስታውቋል።
በአዲስ አበባ በሚገኘው የማዕከሉ ዋና መሥሪያ ቤት ውስጥ የተገነባው ይህ መጋዘን፦
🟠 1,000 ካሬ ሜትር ስፋት አለው፡፡
🟠 ክትባቶችንና መድኃኒቶችን በደህንነት ለማቆየት የሚያስችል የማቀዝቀዣ ሥርዓት የተገጠመለት ነው።
"ይህ አዲስ ማዕከል የበሽታ ወረርሽኝ በሚከሰትበት ጊዜ በብቃትና በተገቢው ፍጥነት ምላሽ ለመስጠት የሚያስችለንን አቅም ይፈጥርልናል" ሲሉ የአፍሪካ ሲዲሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ራጂ ታጁዲን ተናግረዋል፡፡
መጋዘኑ የውጭ ጥገኝነትን ለመቀነስ እና የአኅጉሪቱን የጤና ዋስትና ለማረጋገጥ ወሳኝ ምዕራፍ ነው ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X