የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቋርጦት የነበረውን የመቀሌ በረራ ዳግም አስጀምረ
12:30 03.02.2026 (የተሻሻለ: 12:34 03.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቋርጦት የነበረውን የመቀሌ በረራ ዳግም አስጀምረ
አየር መንገዱ ከጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 5 ቀናት ወደ ትግራይ ክልል የሚደረገውን በረራ አቋርጦ የቆየ ቢሆንም ዛሬ ማክሰኞ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም ዳግም በረራ መጀመሩን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
በበረራው መቋረጥ ሳቢያ ከሰሞኑን እረፍት ላይ የነበሩ የመቀሌ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ ሠራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ መደረጉ ተገልጿል፡፡
ℹ እንደ ፍላይት ራዳር 24 የበረራ መቆጣጠሪያ ድረ ገፅ መሠረት፤ የበረራ ቁጥር ኢቲ102 የሆነ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን ከጠዋቱ ሁለት ሰዓት ከቦሌ አየር ማረፊያ ተነስቶ ወደ መቀሌ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ አቅንቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X