ደቡብ አፍሪካዊቷ አቀንቃኝ ታይላ በ2026 የግራሚ ሽልማት በዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ ሙዚቃ ዘርፍ አሸነፈች
19:03 02.02.2026 (የተሻሻለ: 19:14 02.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካዊቷ አቀንቃኝ ታይላ በ2026 የግራሚ ሽልማት በዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ ሙዚቃ ዘርፍ አሸነፈች
የሙዚቃ ኮከቧ እውቆቹን የናይጄሪያ ድምፃውያን በርና ቦይ፣ ዳቪዶ እና አይራ ስታርን በመርታት በዓመቱ ምርጥ የአፍሪካ ሙዚቃ ሥራ ዘርፍ አሸናፊ ሆናለች።
ታይላ፤ ለሽልማቱ በእጩነት የቀረቡትን የበርና ቦይ "Love"፣ የዳቪዶ "With You"፣ የአይራ ስታር እና ዊዝኪድ "Gimme Dat" እንዲሁም የኤዲ ኬንዞ እና መህራን ማቲን "Hope & Love" የሙዚቃ ሥራዎችን በልጣ ያሸነፈችው "Push 2 Start" በተሰኘው ዘፈኗ ነው።
ይህ ድል ታይላ በፈረንጆቹ 2024 "Water" በተሰኘው ዘፈኗ ሽልማቱን ካገኘች በኋላ በዘርፉ ለሁለተኛ ጊዜ በማሸነፍ የወቅቱ የአፍሪካ ዓለም አቀፍ ኮከብ መሆኗን ይበልጥ ያረጋገጠችበት ሆኗል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/