ሩሲያ እና ብራዚል የባለ ብዙ ዋልታ ዓለም ሥርዓትን ለመፍጠርና ትብብራቸውን ለማጠናከር እየሠሩ ነው - የሩሲያ መንግሥት

ሩሲያ እና ብራዚል የባለ ብዙ ዋልታ ዓለም ሥርዓትን ለመፍጠርና ትብብራቸውን ለማጠናከር እየሠሩ ነው - የሩሲያ መንግሥት
የሩሲያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚካሂል ሚሹስቲን ከብራዚል ፕሬዚዳንት ሉዊዝ ኢናሲዮ ሉላ ዳ ሲልቫ ጋር ለመወያየት ሐሙስ ወደ ብራዚሊያ የሚያደርጉትን ጉብኝት ተከትሎ በወጣው መግለጫ ሩሲያ እና ብራዚል አጋርነታቸውን እያጠናከሩ እንደሚገኙ ተገልጿል።
በስብሰባው ዙሪያ ከሩሲያ መንግሥት የተሰጡ ዋና ዋና መግለጫዎች፦
ሞስኮ እና ብራዚሊያ የባለ ብዙ ዋልታ ዓለም የኃይል ሚዛንን ይደግፋሉ፤ ሉዓላዊነትንና ጣልቃ አለመግባትን በማስቀደም በአንድ ወገን የሚጣሉ ማዕቀቦችን ይቃወማሉ።
መሪዎቹ የከፍተኛ ደረጃ የትብብር ኮሚሽን ስብሰባዎችን የሚያካሂዱ ሲሆን በሁለትዮሽ የንግድ መድረክ ላይም ይታደማሉ።
በመጪዎቹ ዓመታት ቅድሚያ በሚሰጣቸው የትብብር መስኮች ዙሪያ የጋራ መግለጫ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል።
ውይይቱ በኢነርጂ፣ በኢንዱስትሪ፣ በግብርና፣ በትራንስፖርት እና በንግድ ዘርፎች ፕሮጀክቶችን በማስፋፋት ላይ ያተኩራል።
ውይይቶቹ በ2025-2026 በቭላድሚር ፑቲን እና በሉላ መካከል የተደረሱ ስምምነቶችን መሠረት ያደረጉ ይሆናሉ።
ሩሲያ እና ብራዚል በብሪክስ እና በቡድን 20 መድረኮች ያላቸውን ጠንካራ ትብብር ይቀጥላሉ።
የባሕል፣ የሳይንስ፣ የትምህርት እና የስፖርት ልውውጦችም እያደጉ ይገኛሉ።
ሚሹስቲን በጉብኝታቸው ወቅት ከምክትል ፕሬዚዳንት ጄራልዶ አልክሚንም ጋር ይገናኛሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X