በሶማሊያ ፓርላማ ተቃዋሚዎች በሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ድምፅ አሰጣጥ ላይ እንቅፋት በመፍጠራቸው ሁከት ተቀሰቀሰ
17:23 02.02.2026 (የተሻሻለ: 17:34 02.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሶማሊያ ፓርላማ ተቃዋሚዎች በሕገ-መንግሥት ማሻሻያ ድምፅ አሰጣጥ ላይ እንቅፋት በመፍጠራቸው ሁከት ተቀሰቀሰ
ተቃዋሚ የፓርላማ አባላት ወደ አዳራሹ በመግባት፣ መግቢያዎችን በመዝጋት እና በሕገ-መንግሥታዊ ማሻሻያ ላይ ሊደረግ የነበረውን ስብሰባ ለማስተጓጎል የአፈ-ጉባኤውን ወንበር በመያዛቸው ግጭት መፈጠሩን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
◻ በፓርላማ አባላት እና በፀጥታ ኃይሎች መካከል ግጭት መከሰቱ የተነገረ ሲሆን የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል የሆኑት ካደር ዛሬድን ጨምሮ በርካታ የፓርላማ አባላት ጉዳት ደርሶባቸዋል። ካደር ዛሬድ በእግራቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት ምክንያት ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል (ቪዲዮ 2)።
◻ የማይክሮፎን እና የድምፅ መሣሪያዎች በመሰባበራቸው ምክንያት የዕለቱ ስብሰባ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ ተደርጓል።
◻ ተቃዋሚዎች ማሻሻያው ያልተሟላ እና የመንግሥትን የሥልጣን ዘመን ለማራዘም ታስቦ የተዘጋጀ ነው ሲሉ ይከሳሉ፤ የፌዴራል መንግሥቱ ግን ይህን ክስ ውድቅ አድርጓል።
◻ የዛሬው ግጭት የተከሰተው የፓርላማው አመራር ከትናንት በስቲያ የቀድሞ ስብሰባዎችን አስተጓጉለዋል ያላቸውን 18 የፓርላማ አባላት ለማገድ የወሰነውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ከማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኙ ምሥሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/