ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በኮትዲቯር የኮኮዋ ምርት ዋጋ ላይ ያላቸውን ቁጥጥር ለመመከት የመፍትሄ ሃሳብ አቀረቡ
16:16 02.02.2026 (የተሻሻለ: 16:24 02.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በኮትዲቯር የኮኮዋ ምርት ዋጋ ላይ ያላቸውን ቁጥጥር ለመመከት የመፍትሄ ሃሳብ አቀረቡ
ኮትዲቯር የዓለምን 40 በመቶ የኮኮዋ ፍላጎት ብትሸፍንም እንደሌሎች የአፍሪካ አምራቾች ሁሉ በዋጋው ላይ ያላት ቁጥጥር አነስተኛ እና ለተለዋዋጭ የዓለም ገበያ የተጋለጠ ነው።
የኮትዲቯር የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት ፕሪንስ ቤጋንሱ ለስፑትኒክ አፍሪካ በሰጡት አስተያየት፤ ዋናው መፍትሄ ምርቱ ወደ ውጭ ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ የሚቀነባበርበትን መሠረተ ልማት ማልማት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። ይህ ካልሆነ ግን ሀገሪቱ "ዋጋቸውን በላያችን ላይ ለሚጭኑ ዓለም አቀፍ ተቋማት ትዕዛዝ" ተገዢ ሆና ትቀጥላለች ብለዋል።
በሌላ በኩል የምጣኔ ሀብት ተንታኙ ዣን ሉዊ ባግቦ፤ በአምራቾች መካከል ያለው ትብብር ወሳኝ እንደሆነ ገልጸዋል። ለዚህም የኮትዲቯር እና የጋናን የኮኮዋ ጥምረት ለአምራቾች አንድነት በማሳያነት ጠቅሰዋል።
ጥምረቱ "ላኪዎች ወይም ግዙፍ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ተመጣጣኝ የዋጋ ልዩነት እንዲያደርጉ ተጽዕኖ ማሳደር" አስችሏል ሲሉ ተንታኙ አብራርተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X