አፍሪኤግዚም ባንክ ከፊች ጋር ግንኙነት በማቋረጡ 'የገበያ መዛባትን' ይከላከላል - ደቡብ አፍሪካዊው ባለሙያ
19:45 01.02.2026 (የተሻሻለ: 19:54 01.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አፍሪኤግዚም ባንክ ከፊች ጋር ግንኙነት በማቋረጡ 'የገበያ መዛባትን' ይከላከላል - ደቡብ አፍሪካዊው ባለሙያ
የአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ ከአሜሪካ የብድር ደረጃ አውጪ ኤጀንሲ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማቆም መወሰኑ፤ "ቀንደኛ የተሳሳቱ መረጃዎች ምንጭን" ለማስወገድ የተደረገ ስልታዊ እርምጃ ነው ሲሉ ዶ/ር ሚሼክ ሙቲዜ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
ፊች ያልተረጋገጡ የሥስተኛ ወገን ትንታኔዎችን በተለይም የአፍሪካ የባለብዙ ወገን ባንኮች ከሚፈልጉት የአበዳሪነት ደረጃ በተቃራኒው የሚቆመውን የዓለም አቀፉን የገንዘብ ተቋም መረጃዎች ይጠቀማል ሲሉ በአፍሪካ የአቻ ግምገማ አሠራር በኤጀንሲዎች የደረጃ አሰጣጥ የሀገራት ድጋፍ ዋና ባለሙያው አብራርተዋል።
የአፍሪኤግዚም ባንክ ሕጋዊ ከለላዎች የዓለም አቀፍ ሕግ አካል በመሆናቸው ባንኩ ልምድን መሠረት ከሚያደርጉ ተቋማት የበለጠ ጠንካራ አቋም እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ስለዚህ ባንኩ ከኤጄንሲው መውጣቱ ተቋማዊ ባህሪውን የሚያዛቡ እና ገበያውን የሚያሳስቱ ግምገማዎችን እንዲከላከል ያስችለዋል ሲሉ ባለሙያው ደምድመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X