ኢኮዋስ ጊኒ ቢሳው ወደ ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓት ለመመለስ እየወሰደች ያለውን እርምጃ አደነቀ
16:51 01.02.2026 (የተሻሻለ: 16:54 01.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢኮዋስ ጊኒ ቢሳው ወደ ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓት ለመመለስ እየወሰደች ያለውን እርምጃ አደነቀ
የጊኒ ቢሳው የሽግግር ግዜ ፕሬዚዳንት ጄኔራል ሆርታ ኢንታ-አ፤ "አካታች የፖለቲካ ምህዳር ለመፍጠር" የተወሰዱ እርምጃዎችን ለምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) ሊቀመንበር በደብዳቤ ማሳወቃቸውን ድርጅቱ በመግለጫው አስታውቋል።
የተወሰዱት እርምጃዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፦
◻ ሁሉንም ወገኖች ያሳተፈ የሽግግር መንግሥት ማቋቋም፣
◻ ከፖለቲከኛው ፈርናንዶ ዲያስ ዳ ኮስታ ቡድን እና ከጊኒ እና ኬፕ ቨርዴ ነፃነት ፓርቲ የተውጣጡ 10 ተወካዮችን በብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት ውስጥ ማሳተፍ፣
◻ ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች መፍታት እና ለዶሚንጎስ ሲሞስ ፔሬራ የተሻለ የእስር ሁኔታን ማመቻቸት፣
◻ የኢኮዋስ ተልዕኮ ከሀገር እንዲወጣ ቀርቦ የነበረውን ጥያቄ ማንሳት።
"ኢኮዋስ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ሰላማዊ፣ ተዓማኒ እና ወደ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለሚያመራ የሽግግር ሂደት በትብብር እንዲሠሩ ያሳስባል" ሲል መግለጫው አጠቃሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X