በዓለም አቀፍ ደረጃ ያንዣበበው አለመረጋጋት አሳሳቢ እንደሆነ የሩሲያ የጸጥታ ምክር ቤት ፀሐፊ ገለጹ
14:46 01.02.2026 (የተሻሻለ: 14:54 01.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ያንዣበበው አለመረጋጋት አሳሳቢ እንደሆነ የሩሲያ የጸጥታ ምክር ቤት ፀሐፊ ገለጹ
በቤጂንግ ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር የተገናኙት ሰርጌ ሾይጉ፤ በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ዙሪያ የሚታዩ ፈጣን ለውጦች እና በተለያዩ የዓለም አካባቢዎች ሁኔታዎች በፍጥነት እየተባባሱ መምጣታቸውን አፅንኦት ሰጥተዋል።
ሾይጉ በተጨማሪም፤ ሩሲያ የጃፓንን ወታደራዊ እንቅስቃሴ በቅርበት እየተከታተለች እንደሆነ እና በታይዋን ጉዳይ ለቤጂንግ ያላትን ድጋፍ ለቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋንግ ዪ በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ዋንግ ዪ በበኩላቸው፤ ቻይና እና ሩሲያ እጅግ አስፈላጊ በሆኑ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ የጠበቀ ግንኙነታቸውን ሊቀጥሉና የእርስ በእርስ ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X