የሳኅል ሀገራት ጥምረት በኒያሜ የተፈፀመውን የሽብር ጥቃት ‘አረመኔያዊ እና የታቀደ’ ሲል ኮነነ
14:20 01.02.2026 (የተሻሻለ: 14:24 01.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሳኅል ሀገራት ጥምረት በኒያሜ የተፈፀመውን የሽብር ጥቃት ‘አረመኔያዊ እና የታቀደ’ ሲል ኮነነ
የሳኅል ሀገራት ጥምረት እነዚህ ጥቃቶች፤ “አስቀድሞ የታቀዱ፣ የተቀናጁ እና ያለ ልዩነት ስትራቴጂያዊ መሠረተ ልማቶችን እና የሲቪል ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ" መሆናቸውን ያምናል ሲሉ የጥምረቱ ሊቀመንበር ካፒቴን ኢብራሂም ትራኦሬ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።
“ንጹሃን ዜጎችን እና የሲቪል ንብረቶችን” ለአደጋ ያጋለጠው ይህ ጥቃት፤ የተነጠለ ድርጊት ተደርጎ ሊታይ አይችልም ሲል መግለጫው አክሏል።
ድርጊቱ “በውጭ ሀገራት ተዋናዮች ቀጥተኛም ይሁን ቀጥተኛ ያልሆነ ድጋፍ በመጠነ ሰፊ መረቦች የሚታገዝ “የማተራመስ ስትራቴጂ” አካል ነው፡፡ የጥምረቱ ሊቀመንበር እነዚህ አካላቶች የሞራል፣ የፖለቲካ እና የሕግ ተጠያቂነት አለባቸው ብለዋል።
የሳኅል ሀገራት ጥምረት የትኛውንም ዓይነት እብሪት፣ ብዝበዛ ወይም የወንጀል ድጋፍ በቸልታ እንደማያልፍ ትራኦሬ በማጠቃለያቸው አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X