‘ፖሊስ አስፈላጊ ነው፣ ፖሊስን እንወዳለን’ - በፓሪስ ለሕግ አስከባሪ አካላት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

ሰብስክራይብ

ፖሊስ አስፈላጊ ነው፣ ፖሊስን እንወዳለን’ - በፓሪስ ለሕግ አስከባሪ አካላት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ

​የሰልፉ ዓላማ፣ የፖሊስ መኮንኖች የሥራ ሁኔታ መበላሸቱን እና በመንግሥት በኩል የሚቀርበው የሃብት አቅርቦት ማነስን ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለማሳወቅ እንደሆነ በስፍራው የሚገኘው የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።

​በፓሪስ፣ በተካሄደው በዚህ ሰልፍ ላይ አዘጋጆቹ ከ15 ሺህ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች መገኘታቸውን ገልጸዋል። በሰልፉ ላይ በርካታ የፖለቲካ ሰዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል የ"ዴቦት ላ ፍራንስ" ፓርቲ ፕሬዝዳንት እና የጎርጎሮሳዊያኑ 2027 የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ኒኮላ ዱፖንት-አይግናን፣ እንዲሁም የአውሮፓ ፓርላማ አባላቱ ማሪዮን ማሬሻል እና ቲዬሪ ማሪያኒ ይገኙበታል።

​ በዛሬው ዕለት በፈረንሳይ ዋና ግዛቶች በሚገኙ ሃያ ገደማ ከተሞች ተመሳሳይ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0