‘ፖሊስ አስፈላጊ ነው፣ ፖሊስን እንወዳለን’ - በፓሪስ ለሕግ አስከባሪ አካላት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ
20:25 31.01.2026 (የተሻሻለ: 20:34 31.01.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
‘ፖሊስ አስፈላጊ ነው፣ ፖሊስን እንወዳለን’ - በፓሪስ ለሕግ አስከባሪ አካላት የድጋፍ ሰልፍ ተካሄደ
የሰልፉ ዓላማ፣ የፖሊስ መኮንኖች የሥራ ሁኔታ መበላሸቱን እና በመንግሥት በኩል የሚቀርበው የሃብት አቅርቦት ማነስን ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ለማሳወቅ እንደሆነ በስፍራው የሚገኘው የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል።
በፓሪስ፣ በተካሄደው በዚህ ሰልፍ ላይ አዘጋጆቹ ከ15 ሺህ እስከ 20 ሺህ የሚደርሱ ሰዎች መገኘታቸውን ገልጸዋል። በሰልፉ ላይ በርካታ የፖለቲካ ሰዎች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል የ"ዴቦት ላ ፍራንስ" ፓርቲ ፕሬዝዳንት እና የጎርጎሮሳዊያኑ 2027 የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እጩ ኒኮላ ዱፖንት-አይግናን፣ እንዲሁም የአውሮፓ ፓርላማ አባላቱ ማሪዮን ማሬሻል እና ቲዬሪ ማሪያኒ ይገኙበታል።
በዛሬው ዕለት በፈረንሳይ ዋና ግዛቶች በሚገኙ ሃያ ገደማ ከተሞች ተመሳሳይ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X