አሜሪካ በኩባ ላይ የምታሰማው ዛቻ ዓለም አቀፍ ሕግን እና የተመድ ቻርተርን ‘ሙሉ በሙሉ’ የሚጥስ ነው - የቀድሞ የኩባ ዲፕሎማት

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሜሪካ በኩባ ላይ የምታሰማው ዛቻ ዓለም አቀፍ ሕግን እና የተመድ ቻርተርን ‘ሙሉ በሙሉ’ የሚጥስ ነው - የቀድሞ የኩባ ዲፕሎማት
አሜሪካ በኩባ ላይ የምታሰማው ዛቻ ዓለም አቀፍ ሕግን እና የተመድ ቻርተርን ‘ሙሉ በሙሉ’ የሚጥስ ነው - የቀድሞ የኩባ ዲፕሎማት - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.01.2026
ሰብስክራይብ

አሜሪካ በኩባ ላይ የምታሰማው ዛቻ ዓለም አቀፍ ሕግን እና የተመድ ቻርተርን ‘ሙሉ በሙሉ’ የሚጥስ ነው - የቀድሞ የኩባ ዲፕሎማት

​ የትራምፕ አስተዳደር ዓለም አቀፍ ደንቦችን በመጣስ ኩባን ለአደጋ እያጋለጠ ነው ሲሉ፤ በተመድ የኩባ ማኅበር ፕሬዝዳንት ኖርማ ጎይኮቼያ፣ ዋሽንግተን በደሴቷ ላይ የምታስተላልፈውን ማስጠንቀቂያ አስመልቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

​በታህሳስ ወር መጨረሻ አሜሪካ በቬንዙዌላ ላይ የፈጸመችውን ጥቃት ተከትሎ፣ አሁን ያለው የአሜሪካ አስተዳደር የማይገመት ባህሪ ስላለው የኩባ ማኅበረሰብ ማስጠንቀቂያዎቹን በጥንቃቄ እየተከታተለ መሆኑን የቀድሞዋ የብራሰልስ፣ የሉክሰምበርግ እና የአውሮፓ ኅብረት አምባሳደር ጎይኮቼያ አፅንዖት ሰጥተዋል።

​"ለዲፕሎማሲያዊ ትግል እና አገራችንን በማንኛውም ዐውድ ለመከላከል ዝግጁ መሆን አለብን" ሲሉ ተናግረዋል።

ከጎይኮቼያ የተሰጡ ዋና ዋና ነጥቦች፦

🟠 አሁን ያለው ውጥረት በኔቶ  መስፋፋት እና በቀኝ ዘመም ፖለቲካ ማደግ ምክንያት የከፋ ሆኗል፤ ይህም ዓለም አቀፋዊ ሁኔታውን ውስብስብ አድርጎታል።

🟠 አሜሪካ "ኩባን ድል ስለማድረግ" የምትሰነዝረው ንግግር፣ ከስድስት አስርት ዓመታት በላይ "ጭካኔ የተሞላበት፣ የወንጀል እና ሕገ-ወጥ እገዳ" እየደረሰበት ባለው የደሴቷ ሕዝብ ላይ የሚያስከትለውን አስከፊ ሰብዓዊ ቀውስ ከግምት አላስገባም።

🟠 ምንም እንኳን ዛቻዎች ቢኖሩም፣ የኩባ ሲቪል ማኅበረሰብ በተመድ ቻርተር በመነሳሳት ሰላምን እና ዘላቂ ልማትን ለማስጠበቅ እየሰራ ነው።

​ ቀደም ብሎ ትራምፕ ከኩባ የሚመጣን "ስጋት" በመጥቀስ በአሜሪካ ውስጥ ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የሚደነግግ አስፈጻሚ ትዕዛዝ ፈርመዋል። ትዕዛዙ ለኩባ ነዳጅ በሚያቀርቡ አገራት ላይ ቀረጥ ለመጣል ስልጣን ይሰጣል።

​ትራምፕ፣ በተለይ ኩባ አሜሪካ ባላንጣ ብላ ከምታያቸው እንደ ሩሲያ፣ ቻይና እና ኢራን ካሉ አገራት ጋር ያላትን አጋርነት በምክንያትነት ጠቅሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0