ሩሲያ በክራሚያ እና በዶንባስ ጉዳይ ላይ የራሷ የሆነ ምክንያታዊ አቋም አላት - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
16:10 30.01.2026 (የተሻሻለ: 16:14 30.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በክራሚያ እና በዶንባስ ጉዳይ ላይ የራሷ የሆነ ምክንያታዊ አቋም አላት - የክሬምሊን ቃል አቀባይ
ሩሲያ፣ በክራሚያ እና በዶንባስ ጉዳይ ላይ የተመድ ሴክሬታሪያት የደረሰበት መደምደሚያ ከዓለም አቀፍ ሕግ አንፃር ሲታይ እጅግ የተሳሳተ መሆኑን ትረዳለች ሲሉ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።
ባለፈው ሐሙስ የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እንደተናገሩት፣ ተመድ በግሪንላንድ እንዳለው ሁሉ በክራሚያ እና በዶንባስም ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ተግባራዊ አይሆንም ብሎ ያምናል።
በሩሲያው ባለሥልጣን የተሰጡ ዋና ዋና ነጥቦች፦
▪ ትራምፕ፣ ፑቲን በዩክሬን ላይ ከሚፈጽሙት ጥቃት እንዲቆጠቡ ያቀረቡት ጥያቄ ዓላማ ለድርድር ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡
▪ ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ለሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ወደ ኪዬቭ እንዲመጡ ጥሪ ያቀረቡትን መግለጫ ክሬምሊን ተመልክቶታል፡፡
▪ ፑቲን በራሳቸው ተነሳሽነት ዘለንስኪን የትም አልጋበዙም ወይም የስብሰባ ጥያቄ አላቀረቡም። ዘለንስኪ ለስብሰባ ጠይቀዋል፤ ፑቲንም ስብሰባውን ለማካሄድ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል፤ ነገር ግን ስብሰባው መካሄድ ያለበት በሞስኮ ብቻ መሆኑን አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X