ናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ
ናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.01.2026
ሰብስክራይብ

ናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ

​ የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ቤሎ ማታዋሌ እንደገለፁት፣ ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር የሀገር ውስጥ የመከላከያ ኢንዱስትሪዋን በማጠናከር ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ከውጭ የማስገባት ጥገኝነትን ለማቆም አቅዳለች።

​ይህ ዕቅድ ይፋ የተደረገው፣ “የኤክስ-ሺልድ ሶልዩሽንስ” ኩባንያ አቡጃ ውስጥ ዲዛይን ያደረገው አገር በቀል “ቀላል ታክቲካል ብረት ለበስ ተሽከርካሪ” ምርቃት ላይ ነው።

​ ማታዋሌ እ.ኤ.አ. በ2023 የናይጄሪያ መከላከያ ኢንዱስትሪዎች ኮርፖሬሽን (ዲአይኮን) አዋጅ ለዚህ ስራ እንደ ትልቅ አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፣ የወደፊት የመከላከያ አቅሞች በኢንዱስትሪ አጋርነቶች አማካኝነት በአገር ውስጥ እንደሚገነቡ አፅንዖት ሰጥተዋል።

​የ“ኤክስ- ሺልድ” ዋና ስራ አስፈፃሚ ቻርለስ ኢባንጋ እንደገለጹት፣ በዲአይኮን እና እንደ "ኤክስ-ሺልድ" ባሉ የግል ኩባንያዎች መካከል ያለው ትብብር ወደ ንግድ ዘላቂነት ለመሸጋገር እና የገቢ ምርቶች ጥገኝነትን ለመቀነስ ወሳኝ ነው።

​ እንደ ባለስልጣናት ገለጻ፣ ናይጄሪያ በአሁኑ ወቅት በአገር ውስጥ የተመረቱ አንዳንድ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለሌሎች የአፍሪካ አገራት በመላክ ላይ ትገኛለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0