ናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ
15:40 30.01.2026 (የተሻሻለ: 15:44 30.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ በአምስት ዓመታት ውስጥ በመከላከያ ዘርፍ ራሷን የመቻል ዕቅድ አላት ሲሉ ሚኒስትሩ አስታወቁ
የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ቤሎ ማታዋሌ እንደገለፁት፣ ምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር የሀገር ውስጥ የመከላከያ ኢንዱስትሪዋን በማጠናከር ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ከውጭ የማስገባት ጥገኝነትን ለማቆም አቅዳለች።
ይህ ዕቅድ ይፋ የተደረገው፣ “የኤክስ-ሺልድ ሶልዩሽንስ” ኩባንያ አቡጃ ውስጥ ዲዛይን ያደረገው አገር በቀል “ቀላል ታክቲካል ብረት ለበስ ተሽከርካሪ” ምርቃት ላይ ነው።
ማታዋሌ እ.ኤ.አ. በ2023 የናይጄሪያ መከላከያ ኢንዱስትሪዎች ኮርፖሬሽን (ዲአይኮን) አዋጅ ለዚህ ስራ እንደ ትልቅ አጋዥ መሆኑን ጠቅሰው፣ የወደፊት የመከላከያ አቅሞች በኢንዱስትሪ አጋርነቶች አማካኝነት በአገር ውስጥ እንደሚገነቡ አፅንዖት ሰጥተዋል።
የ“ኤክስ- ሺልድ” ዋና ስራ አስፈፃሚ ቻርለስ ኢባንጋ እንደገለጹት፣ በዲአይኮን እና እንደ "ኤክስ-ሺልድ" ባሉ የግል ኩባንያዎች መካከል ያለው ትብብር ወደ ንግድ ዘላቂነት ለመሸጋገር እና የገቢ ምርቶች ጥገኝነትን ለመቀነስ ወሳኝ ነው።
እንደ ባለስልጣናት ገለጻ፣ ናይጄሪያ በአሁኑ ወቅት በአገር ውስጥ የተመረቱ አንዳንድ ወታደራዊ ቁሳቁሶችን ለሌሎች የአፍሪካ አገራት በመላክ ላይ ትገኛለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X