ከሁለት ሚሊዮን ዓመታት በፊት ከአፍሪካ ውጭ የሰው ልጅ አልነበረም - አንጋፋው የቅድመ ሰው ጥናት ተመራማሪ

ሰብስክራይብ

ከሁለት ሚሊዮን ዓመታት በፊት ከአፍሪካ ውጭ የሰው ልጅ አልነበረም - አንጋፋው የቅድመ ሰው ጥናት ተመራማሪ

ዘረሰናይ ዓለምሰገድ (ፕ/ር) ፤ በቅርቡ በእርሳቸው በተመራ ቡድን በአፋር ክልል ሚሌ-ሎጊያ የፓሊዮአንትሮፖሎጂ መካነ ቅርስ ሥፍራ የተገኘው 'ፕራንትሮፐስ' የተሰኘው የጥንታዊ የሰው ዘር ቅሪት አካል፣ የአፍሪካን በተለይም የኢትዮጵያን የሰው ዘር መገኛነት ይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑን ይገልጻሉ።

የ'ፓራንትሮፐስ’ ቅሪት በአፋር ክልል ሲገኝ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ያነሱት በአሜሪካ ቺካጎ ዩኒቨርሲቲ የዘርፉ ተመራማሪው፣ ስለ ቀደምት ግኝቶቻቸውም ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

"ከተሳተፍኩባቸው ሥራዎች መካከል አንዱ የ'ሰላም’ መገኘት ነው። ይህ አፅም ከታዋቂዋ ‘ሉሲ’ (ድንቅነሽ) በ200 ሺህ ዓመት የሚቀድም ብቻ ሳይሆን 60 በመቶም የተሟላ ነው፡፡ ሌላኛው ግኝቴ በአፋር ክልል 'ዲኪካ' በተባለ ሥፍራ የተገኘው የመጀመሪያው የድንጋይ መሣሪያ ማስረጃ ነው።" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0