ኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ
ኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.01.2026
ሰብስክራይብ

ኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ

ይህ ውሳኔ የጊኒ የሽግግር ወቅት ማብቃቱን እና ሀገሪቱ ወደ ቀጣናዊው ማኅበረሰብ ሙሉ በሙሉ መመለሷን በይፋ የሚያበስር ነው።

ጊኒ በሁሉም የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) የውሳኔ ሰጪ አካላት ውስጥ መቀመጫዋን መልሳ ያገኘች ሲሆን፣ በቀጣናዊ የትስስር እንቅስቃሴዎች ላይ ያላትን ተሳትፎም ትቀጥላለች።

ኢኮዋስ በመስከረም 11 የተካሄደውን የሕገ-መንግሥት ሕዝበ ውሳኔ እና በታኅሣሥ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ስኬታማ ውጤቶች አድንቋል።

ድርጅቱ ማማዲ ዱምቡያ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት በመሆን በዓለ ሲመታቸውን በማከናወናቸው ይፋዊ የእንኳን ደስ አለዎት መልእክት አስተላልፏል።

ኢኮዋስ በመጪው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ ከመካሄዱ በፊት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ትስስርን ለማረጋገጥ የጊኒ መንግሥት ብሔራዊ ምክክሩን እንዲቀጥል አበረታቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0