ኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ
16:55 29.01.2026 (የተሻሻለ: 17:04 29.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢኮዋስ በጊኒ ላይ ጥሎት የነበረውን ማዕቀብ ሙሉ በሙሉ አነሳ
ይህ ውሳኔ የጊኒ የሽግግር ወቅት ማብቃቱን እና ሀገሪቱ ወደ ቀጣናዊው ማኅበረሰብ ሙሉ በሙሉ መመለሷን በይፋ የሚያበስር ነው።
ጊኒ በሁሉም የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) የውሳኔ ሰጪ አካላት ውስጥ መቀመጫዋን መልሳ ያገኘች ሲሆን፣ በቀጣናዊ የትስስር እንቅስቃሴዎች ላይ ያላትን ተሳትፎም ትቀጥላለች።
ኢኮዋስ በመስከረም 11 የተካሄደውን የሕገ-መንግሥት ሕዝበ ውሳኔ እና በታኅሣሥ የተካሄደውን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ስኬታማ ውጤቶች አድንቋል።
ድርጅቱ ማማዲ ዱምቡያ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት በመሆን በዓለ ሲመታቸውን በማከናወናቸው ይፋዊ የእንኳን ደስ አለዎት መልእክት አስተላልፏል።
ኢኮዋስ በመጪው የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ ከመካሄዱ በፊት፣ ዘላቂ ማኅበራዊ ትስስርን ለማረጋገጥ የጊኒ መንግሥት ብሔራዊ ምክክሩን እንዲቀጥል አበረታቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X