ዋሽንግተን እና ኪዬቭ ስለተስማሙባቸው የደኅንነት ዋስትናዎች ሩሲያ የምታውቀው ነገር የለም - ላቭሮቭ
15:40 29.01.2026 (የተሻሻለ: 15:44 29.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ዋሽንግተን እና ኪዬቭ ስለተስማሙባቸው የደኅንነት ዋስትናዎች ሩሲያ የምታውቀው ነገር የለም - ላቭሮቭ
ሞስኮ ትኩረት የምታደርገው በ"ይፋዊ ጨዋታዎች (ፕሮፓጋንዳዎች)" ላይ ሳይሆን በተግባራዊ ስምምነቶች ላይ እንደሚሆን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ቀደም ሲል የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ ለዩክሬን በሚሰጡ የደኅንነት ዋስትናዎች ላይ አጠቃላይ ስምምነት መደረሱን ገልጸው ነበር።
ሩቢዮ አክለውም፣ ለወደፊቱ ለዩክሬን የሚሰጡት የደኅንነት ዋስትናዎች በአሜሪካ የሚደገፉ ቢሆንም፣ "በመሬት ላይ" ሊሰማሩ የሚችሉት ግን የአውሮፓ ወታደሮች ብቻ እንደሆኑ ጠቁመዋል።
ለዩክሬን የተዘጋጀው የደኅንነት ዋስትና ሥርዓት ውጤታማነቱ በአሜሪካ ድጋፍ ላይ የተመሠረተ መሆኑንም ሩቢዮ ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X