ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ85 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
13:56 29.01.2026 (የተሻሻለ: 14:04 29.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮ ቴሌኮም በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት ከ85 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
በዚህም የእቅዱን 81 በመቶ ማሳካቱንም ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ የ2018 በጀት ግማሽ ዓመት አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ላይ ገልጸዋል፡፡
የደንበኞቹ ቁጥር 87.1 ሚሊዮን መድረሱን መናገራቸውንም የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግባለች፡፡
በዋና ሥራ አስፈጻሚዋ የተሰጡ ተጨማሪ መግለጫዎች፦
በቴሌብር 1.94 ትሪሊዮን ብር የገንዘብ ዝውውር ተካሂዷል።
የግብይት መጠን 1 ቢሊዮን ደርሷል።
የቴሌብር ደንበኞች ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ተሻግሯል።
1.6 ሚሊዮን ዶላር በቴሌብር አማካኝነት ሬሚታንስ አስገኝቷል።
4.2 ሚሊዮን ደንበኞች 8.6 ቢሊዮን ብር የብድር አገልግሎት አግኝተዋል።
5 ሚሊዮን ደንበኞች ደግሞ 33 ቢሊዮን ብር ቆጥበዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/