ሩሲያ በአፍሪካ የሚዲያ ልማትን ለመደገፍ ለዩኔስኮ የመገናኛ ብዙሃን ልማት ፕሮግራም ያደረገችው የበጎ ፈቃድ አስተዋፅኦ
20:36 28.01.2026 (የተሻሻለ: 12:30 30.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በአፍሪካ የሚዲያ ልማትን ለመደገፍ ለዩኔስኮ የመገናኛ ብዙሃን ልማት ፕሮግራም ያደረገችው የበጎ ፈቃድ አስተዋፅኦ
"ይህ የ250 ሺህ ዶላር አስተዋፅኦ የተደረገው በሩሲያ መንግሥት ትዕዛዝ መሠረት በቋሚ ተልዕኮው በኩል ነው። [...] የሩሲያ የገንዘብ ድጋፎች በማሊ፣ ማላዊ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ሴኔጋል እና ኔፓል ውስጥ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር እየዋሉ ነው፡፡ እነዚህም ለዩኔስኮ ተዛማጅ ማመልከቻዎችን አስገብተዋል" ሲሉ በድርጅቱ የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ሪናት አሊያውትዲኖቭ ለሩሲያ ሚዲያ ተናግረዋል።
በገንዘብ ልገሳው የሚደግፋቸው ፕሮጀክቶች የሚከተሉትን ለማድረግ ታስበው የተነደፉ ናቸው፦
🟠 የጋዜጠኞችን ሙያዊ ብቃት ማሳደግ፣
🟠 የኦንላይን ጥቃትን መዋጋት፣
🟠 የሚዲያ እና የመረጃ እውቀትን ማዳበር።
የሩሲያ የገንዘብ ድጋፍ በኔፓል ጥያቄ መሠረት የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ሥልጠና ፕሮግራምንም ይደግፋል።
ፕሮጀክቶቹ በሚቀጥሉት 18 ወራት ውስጥ ተግባራዊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሩሲያ ከግሎባል ሳውዝ ሀገራት ጋር በመረጃ ዘርፍ ትብብርን ማጠናከር ላይ ከፍተኛ ትኩረት ትሰጣለች። እንዲሁም በዓለም አቀፍ የኮሙኒኬሽን ልማት ፕሮግራም (IPDC) ማዕቀፍ ውስጥ "ምርጥ ልምዶችን ትጋራለች፣ የጋዜጠኞችን መብት ትደግፋለች፣ ስለ ደህንነታቸው ትሟገታለች እንዲሁም ወዳጃዊ ከሆኑ ሀገራት አጋሮችን በሚዲያ ልማት ትረዳለች" ሲሉ አሊያውትዲኖቭ ገልፀዋል።
"ሩሲያ በታሪካዊ ትስስር እና በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ እያደገ በመጣው የአፍሪካ ሚና የተነሳ፣ ከአኅጉሪቱ ሀገራት ጋር ትብብርን በንቃት እያሳደገች ነው።"
የሩሲያ-አፍሪካ አጋርነት ፎረም ሁለተኛው የሚኒስትሮች ጉባኤ ተሳታፊዎች በካይሮ ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ፣ በዩኔስኮ ማዕቀፍ ውስጥ ጨምሮ የሩሲያ-አፍሪካን ሰብአዊ ትብብር ማስፋት አስፈላጊነት ተንፀባርቋል ሲሉ አሊያውትዲኖቭ አስታውቀዋል።
በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምፆች አጉልቶ ማሰማትን፣ የአፍሪካን እድገት፣ ወጎች እና ባሕል ለማጋራት የሚዲያ ልማትን ማስተዋወቅ እንደሚደግፉአክለዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
"ይህ የ250 ሺህ ዶላር አስተዋፅኦ የተደረገው በሩሲያ መንግሥት ትዕዛዝ መሠረት በቋሚ ተልዕኮው በኩል ነው። [...] የሩሲያ የገንዘብ ድጋፎች በማሊ፣ ማላዊ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ሴኔጋል እና ኔፓል ውስጥ ፕሮጀክቶችን ለመተግበር እየዋሉ ነው፡፡ እነዚህም ለዩኔስኮ ተዛማጅ ማመልከቻዎችን አስገብተዋል" ሲሉ በድርጅቱ የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ሪናት አሊያውትዲኖቭ ለሩሲያ ሚዲያ ተናግረዋል።
በገንዘብ ልገሳው የሚደግፋቸው ፕሮጀክቶች የሚከተሉትን ለማድረግ ታስበው የተነደፉ ናቸው፦
🟠 የጋዜጠኞችን ሙያዊ ብቃት ማሳደግ፣
🟠 የኦንላይን ጥቃትን መዋጋት፣
🟠 የሚዲያ እና የመረጃ እውቀትን ማዳበር።
የሩሲያ የገንዘብ ድጋፍ በኔፓል ጥያቄ መሠረት የጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር ሥልጠና ፕሮግራምንም ይደግፋል።
ፕሮጀክቶቹ በሚቀጥሉት 18 ወራት ውስጥ ተግባራዊ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ሩሲያ ከግሎባል ሳውዝ ሀገራት ጋር በመረጃ ዘርፍ ትብብርን ማጠናከር ላይ ከፍተኛ ትኩረት ትሰጣለች። እንዲሁም በዓለም አቀፍ የኮሙኒኬሽን ልማት ፕሮግራም (IPDC) ማዕቀፍ ውስጥ "ምርጥ ልምዶችን ትጋራለች፣ የጋዜጠኞችን መብት ትደግፋለች፣ ስለ ደህንነታቸው ትሟገታለች እንዲሁም ወዳጃዊ ከሆኑ ሀገራት አጋሮችን በሚዲያ ልማት ትረዳለች" ሲሉ አሊያውትዲኖቭ ገልፀዋል።
"ሩሲያ በታሪካዊ ትስስር እና በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ እያደገ በመጣው የአፍሪካ ሚና የተነሳ፣ ከአኅጉሪቱ ሀገራት ጋር ትብብርን በንቃት እያሳደገች ነው።"
የሩሲያ-አፍሪካ አጋርነት ፎረም ሁለተኛው የሚኒስትሮች ጉባኤ ተሳታፊዎች በካይሮ ባወጡት የጋራ መግለጫ ላይ፣ በዩኔስኮ ማዕቀፍ ውስጥ ጨምሮ የሩሲያ-አፍሪካን ሰብአዊ ትብብር ማስፋት አስፈላጊነት ተንፀባርቋል ሲሉ አሊያውትዲኖቭ አስታውቀዋል።
በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የአፍሪካን ድምፆች አጉልቶ ማሰማትን፣ የአፍሪካን እድገት፣ ወጎች እና ባሕል ለማጋራት የሚዲያ ልማትን ማስተዋወቅ እንደሚደግፉአክለዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X