ሞሪሺየስ በቻጎስ ደሴቶች በሚገኘው የእንግሊዝ እና የአሜሪካ የጋራ ጦር ሰፈር ላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይሰማራ ልታግድ መሆኑ ተዘገበ

ሞሪሺየስ በቻጎስ ደሴቶች በሚገኘው የእንግሊዝ እና የአሜሪካ የጋራ ጦር ሰፈር ላይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያ እንዳይሰማራ ልታግድ መሆኑ ተዘገበ
እ.አ.አ ጥቅምት 3 ቀን 2024 እንግሊዝ ዲዬጎ ጋርሺያን ጨምሮ በሕንድ ውቅያኖስ የሚገኙትን የቻጎስ ደሴቶች ሉዓላዊነት ለሞሪሺየስ ለማስተላለፍ መስማማቷን አስታውቃ ነበር። በደሴቲቱ ላይ የእንግሊዝ እና የአሜሪካ የጋራ ወታደራዊ ሰፈር ይገኛል። በስምምነቱ መሠረት ለንደን የጦር ሰፈሩን ለ99 ዓመታት በቁጥጥሯ ስር ታቆያለች።
የመገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት፣ የሞሪሺየስ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ፖል ቤሬንገር ዋቢ ያደረጉት፣ አፍሪካን ከኒውክሌር ጦር መሣሪያ ነፃ ቀጣና አድርጎ የደነገገውን የ1996ቱን የፔሊንዳባ ስምምነት ነው። ቤሬንገር እንዳሉት ስምምነቱ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማከማቸት እና መሞከርን የሚከለክል ቢሆንም፣ በአፍሪካ ሀገራት በኩል ተጭነው ማለፋቸውን ግን አይከለክልም።
ቀደም ሲል የእንግሊዝ ባለሥልጣናት የደሴቶቹ ሉዓላዊነት መተላለፍ በወታደራዊ ካምፑ ሥራ ላይ የሚያመጣው ተጽዕኖ እንደሌለ ገልጸው ነበር።
ሆኖም ባለፈው እሁድ የወጡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፤ አሜሪካ የቻጎስ ደሴቶችን ለሞሪሺየስ የመስጠቱን ስምምነት ውድቅ ልታደርገው ትችላለች። ቀደም ሲል በእንግሊዝ እና በአሜሪካ መካከል በተደረገ ወታደራዊ ስምምነት ምክንያት የአሜሪካ ይሁንታ የግድ አስፈላጊ ነው። በተጨማሪም ስምምነቱ እስካሁን በእንግሊዝ ፓርላማ አልጸደቀም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X