በአዲስ አበባ ዘመናዊ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የእንስሳት ተዋጽኦ ማቀዝቀዣ መጋዘንና ሁለገብ ሕንጻ ተመረቀ
19:47 27.01.2026 (የተሻሻለ: 19:54 27.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ ዘመናዊ የአትክልትና ፍራፍሬ፣ የእንስሳት ተዋጽኦ ማቀዝቀዣ መጋዘንና ሁለገብ ሕንጻ ተመረቀ
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ1.75 ቢሊዮን ብር ወጪ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ያስገነባው ይህ ህንፃ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተመርቋል፡፡
ዛሬ የተመረቀው አዲስ ሁለገብ ህንፃ፦
ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ አስር ወለሎች፣
አስር መጋዘን፣
በአንድ ግዜ ከ20 ሺህ ኩንታል በላይ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም የእንስሳት ተዋጽኦን የማቀዝቀዝ አቅም እንዳለው ተመላክቷል፡፡
“በቀጣይ መሠረታዊ ሸቀጦችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰባችን ተደራሽ ለማድረግ፣ የገበያ ትስስርን ለማጠናከር፣ ንግድን የሚያሳልጡ ዘመናዊ ሎጂስቲክን በማስፋፋትና የሀገራችንን የንግድ ከባቢ ለማዘመን ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን እንሠራለን” ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጉፌ በማኅበራዊ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


