ኢትዮጵያ የነዳጅ ምርቶችን በባቡር የማጓጓዝ ሙከራ ዛሬ ትጀምራለች ተባለ
15:55 27.01.2026 (የተሻሻለ: 16:04 27.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የነዳጅ ምርቶችን በባቡር የማጓጓዝ ሙከራ ዛሬ ትጀምራለች ተባለ
ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ደቡባዊ ዳርቻ ከሚገኘው የንዶዴ የባቡር ዴፖ በሚጀመረው የሙከራ ሂደት፤ 120 ሺህ ሊትር ናፍጣ እንደሚጓጓዝ ተሰምቷል።
ዳራ፦ የኢትዮ ጂቡቲ የምድር ባቡር አክሲዮን ማኅበር ሚያዚያ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ በቦቴ የሚገባው ነዳጅ ከያዝነው ዓመት ጀምሮ ሙሉ ለሙሉ በባቡር እንደሚጓጓዝ አስታውቆ ነበር፡፡
ዕቅድ፦ በቀን እስከ አስር ጊዜ በባቡር በመመላለስ በዓመት 4.2 ሚሊዮን ቶን ነዳጅ ለማጓጓዝ እንደታቀደ ተገልጿል፡፡ እዚህ ላይ የኢትዮ-ጂቡቲ ባቡር መስመር በሰዓት 37 ኪ.ሜ የነበረውን የጉዞ ፍጥነት ወደ 60 ኪ.ሜ እንዳሳደገ ማስታወሱ ተገቢ ነው፡፡
የሚጠበቀው ውጤት
የነዳጅ አቅርቦት ችግርን መቅረፍ፣
የነዳጅ ማጓጓዣ ጊዜን መቀነስ፣
የነዳጅ ዋጋ ላይ ቅናሽ ቅናሽ ማምጣት፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በጅቡቲ ዶራሌ የሚገኘውን የሆራይዘን ተርሚናል በጎበኙበት ወቅት፤ ነዳጅ በአስቸኳይ በባቡር መስመር እንዲጓጓዝ መመሪያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X