ኢንዱስትሪዎች የሀገር ውስጥ ምርቶችን እንዲጠቀሙ የሚያግዙ ማበረታቻዎች ተፈጻሚ እየተደረጉ ነው - ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
14:27 27.01.2026 (የተሻሻለ: 14:34 27.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢንዱስትሪዎች የሀገር ውስጥ ምርቶችን እንዲጠቀሙ የሚያግዙ ማበረታቻዎች ተፈጻሚ እየተደረጉ ነው - ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር
ይህ ይተገለጸው 6ኛው ፊንቴክስ የቤት ዕቃዎች፣ ቤተ-ውበትና የግንባታ አጨራረስ አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረበት ወቅት ነው፡፡
አውደ ርዕዩ አምራቾች እና አስመጪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ለገበያ የሚያስተዋውቁበት መድረክ እንደሆነ የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግቧል፡፡
በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የተኪ ምርቶች ተወዳዳሪነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ መሳይ ውብሸት “መንግሥት የገቢ ምርቶችን እና ወጪ ምርቶችን ለማመጣጠን በትኩረት እየሠራ ነው” ሲሉ በመድረኩ መክፈቻ ላይ ተናግረዋል፡፡
ከጥር 19 እስከ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው አውደ ርዕይ፤ ከ50 በላይ የሀገር ውስጥ ኩባንያዎች እና ከ4ሺህ በላይ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት እንደሚሳተፉ ተገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X



