የሩሲያ ባሕል ማዕከል በኮንጎ ሪፐብሊክ እና ታንዛኒያ የተማሪዎችን ቀን አከበረ
የሩሲያ ባሕል ማዕከል በኮንጎ ሪፐብሊክ እና ታንዛኒያ የተማሪዎችን ቀን አከበረ
በዳሬሰላም፤ ታንዛኒያውያን ተማሪዎች እና የሩሲያ ነፃ የትምህርት ዕድል ተጠቃሚዎች በሩሲያ ስላለው የተማሪዎች ሕይወት ግንዛቤ ለማግኘት ተሰባስበዋል። ተሳታፊዎቹ የባሕል ልውውጥ ያደረጉ ሲሆን የመጀመሪያቸውን "የሩሲያ ዘይቤ" ፈተና በመውሰድ የዓለም አቀፉ አካዳሚክ ማኅበረሰብ አባልነታቸውን በተግባር ሞክረዋል።
በብራዛቪል፤ ተማሪዎች የሩሲያ ባሕል ማዕከልን ለአንድ ቀን በመረከብ የራሳቸውን እንቅስቃሴዎች መርተዋል። በዕለቱም የቋንቋ ትምህርቶችን እና በሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች ስላለው ባሕል ገለጻዎችን አቅርበዋል። ተሳታፊዎቹ "የሪኮርድ ደብተር" የተረከቡም ሲሆን እንደ መኝታ ቤት፣ ስኮላርሺፕ እና የፈተና ወቅት ያሉ ቁልፍ ቃላትን ተምረዋል።
ከዕለቱ ዋና ዋና ክንውኖች አንዱ የሩሲያ ተማሪዎች በተለምዶ ፈተና እንዲቀልላቸው "ፍሪቢ፣ ና!" (Freebie, come!) እያሉ የሚያሰሙትን የልመና ጩኸት በጨዋታ መልክ ያሳዩበት ነበር።
በተጨማሪም በሩሲያ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በትውልድ ሀገራቸው እንዴት የሥራ እና የአመራር ዕድሎችን እንዳገኙ ልምዳቸውን ያካፈሉበት የወጣት መሪዎች ጉባኤ ተካሂዷል።
እ.ኤ.አ ጥር 25 ቀን በሩሲያ "የተማሪዎች ቀን" ወይም "የታቲያና ቀን" ተብሎ ይከበራል። ዕለቱ የተማሪዎች ጠባቂ ተደርጋ የምትታሰበው የቅድስት ታቲያና መታሰቢያ እና እ.ኤ.አ በ1755 የሞስኮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበት ቀን ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X