ጀማሪ አየር ኃይሎች የኢትዮጵያ አየር ኃይል ካካበተው የዳበረ ልምድ መማር ይችላሉ - የዛምቢያ አየር ኃይል ልዑክ

ሰብስክራይብ

ጀማሪ አየር ኃይሎች የኢትዮጵያ አየር ኃይል ካካበተው የዳበረ ልምድ መማር ይችላሉ - የዛምቢያ አየር ኃይል ልዑክ

የኢትዮጵያ አየር ኃይልን 90ኛ ዓመት በዓል በማስመልከት በቢሾፍቱ በተካሄደው “ጥቁር አንበሳ" የአየር ትርዒት ላይ የተገኙት ብ/ጄኔራል ኮሊንስ ንጉሉቤ፤ ዝግጀቱ የአፍሪካ ሀገራትን የአየር ኃይል አቅም ለማስተባበር ዕድል ይፈጥራል ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የአፍሪካ ሀገራት በአየር ኃይል ዘርፍ ያሉባቸው ተግዳሮቶችን መፍታት የሚያስችሉ የክህሎት እና ቴክኖሎጂ የሽግግር መድረኮችን ማስፋት እንዳለባቸውም አክለዋል፡፡

"የኢትዮጵያ አየር ኃይል ቀዳሚ ከሚባሉት እና ከፍተኛ ልምድ ካካበቱ አየር ኃይሎች አንዱ ነው። አዲስ የአየር ኃይሎች ከተቋሙ የሚማሩት ብዙ ልምድ እንዳለም አምናለሁ። መሰል መድረኮች ሀገራት የአየር ኃይላቸውን ይበልጥ ማዘመን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የሚመክሩበትን ዕድል ይፈጥራሉ" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0