ኢትዮጵያ ባሕር ኃይሏን በሥልጠና ለማጠናከር ከደቡብ አፍሪካ እና ሩሲያ ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት ደረሰች
15:34 26.01.2026 (የተሻሻለ: 15:44 26.01.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ባሕር ኃይሏን በሥልጠና ለማጠናከር ከደቡብ አፍሪካ እና ሩሲያ ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት ደረሰች
በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ በነበረው የብሪክስ ሀገራት ዊል ፎር ፒስ (Will For Peace 2026) የባሕር ልምምድ ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ልዑካን ቡድን ወደ ሀገሩ ተመልሷል፡፡
ኢትዮጵያ በልምምዱ በቀጣይ ከብሪክስ ሀገራት ጋር የሚኖራትን ግንኙነት ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚጠቅሙ ግብዓቶች እንዳገኘችበት የልዑካን ቡድኑ መሪ ምክትል አድሚራል ክንዱ ገዙ ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል አዛዥ ከልምምዱ ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካ ባሕር ኃይል አቻቸውና ከሩሲያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት እንዳደረጉ እና የኢትዮጵያን ባሕር ኃይል በተለያዩ የሥልጠና ዘርፎች ለመደገፍ የሁለትዮሽ ስምምነት ላይ እንደደረሱ ከኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የተገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

